ETHIOPIANS TODAY, ADDIS ABABA (FINFINNEE), ETHIOPIA:
375 total views, 1 views today
EthiopiaCheck Exclusive
“መረጃው የተሳሳተ ነው”— የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ለኢትዮጵያ ቼክ
ከ173 ሺህ በላይ ተከታዮች ያሉት ግዕዝ ሚዲያን ጨምሮ አንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የመቐለ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በቀይ መስቀል በኩል እንዲወጡ እንደሚደረግ የሚገልጹ መረጃዎችን ሲያሰራጩ ተመልክተናል።
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከላይ የተጠቀሰው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን ዛሬ ለኢትዮጵያ ቼክ አስታውቋል።
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ወይዘሮ አመለወርቅ ህዝቅኤል መረጃው የተሳሳተ መሆኑን ገልጸው ወላጆችና ህብረተሰቡ የሚመለከታቸው አካላት ብቻ የሚሰጡትን መረጃ እንዲከታተሉ መክረዋል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ትናንት ምሽት በሰጠው መግለጫ በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች የሚማሩ ተማሪዎችን በተመለከ ከተለያዩ አካላት፣ የየዩኒቨርስቲዎቹ አመራሮች እና ከዓለም አቀፍ ተራድኦ ተቋማት ጋር በመሆን እየሰራ እንደሚገኝ መግለጹ ይታወቃል።
ከዩኒቨርስቲዎች አመራር ጋር መገናኘት መቻሉንና ተማሪዎች በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኙም ማወቅ መቻሉን መግለጹም ይታወቃል።
Follow us on:
Telegram: https://t.me/ethiopianstoday
Facebook: https://www.facebook.com/ethiopianstoday
Twitter: https://twitter.com/ethiopianstoday
Instagram: https://www.instagram.com/ethiopianstoday1
Pinterest: https://www.pinterest.com/ethiopianstoday
YouTube: https://www.youtube.com/channel/UC8CrAEUV9Buhu1qaKgptscQ
Google News: https://news.google.com/publications/CAAqBwgKMMf5qQswuYTCAw